የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ.) የ2014ዓ.ም በጀት አመት (2021/22)የዲሬክተሮች ቦርድ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት
አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ በ2014 በጀት አመት ከግብር በፊት ያገኘውን ትርፍ አስታወቀ

አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ በ2014 በጀት አመት ከግብር በፊት ያገኘውን ትርፍ አስታወቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ተቋማዊ አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ምልመላና ምርጫ አፈፃፀም መመሪያ” መሠረት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ቅዳሜ ጥቅምት 19 ቀን 2015 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል፡፡
በዚሁ መሠረት በእለቱ በተካሄደው ምርጫ መሠረት የጉባኤው ጽ/ቤት አባል የሆኑ ድምፅ ቆጣሪዎች፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምልመላና ምርጫ ኮሚቴ እና የሠነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ተወካይ በተገኙበት፤ በሁሉም ባለአክሲዮኖች የጠቆሙና የተመረጡ 12 እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙና የተመረጡ 6 እጩዎች በአጠቃላይ በ18 እጩዎች መካከል በተካሄደ ምርጫና የድምፅ ቆጠራ በእጩዎቹ ስም ትይዩ የተገለፀውን ድምፅ ያገኙ ሲሆን፣ በተገኘው ውጤትም፡-
በሁሉም ባለአክሲዮኖች የተመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች ብቻ የመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ መሠረት ለሚቀጥሉ ሦስት ዓመታት የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ሆነው እንዲሰሩ፣ እንዲሁም በሁለቱም ምድብ በቂ ድምፅ ያላገኙት እጩዎች በየምድባቸው እንደ ቅድመተከተላቸው በተጠባባቂነት እንዲያዙ፤ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምመላ እና ምርጫ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ የወሰነ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ደረጃ | የእጩዎች ሙሉ ስም | የባለአክስዮኖች የጋራ ድምፅ | ምርመራ |
---|---|---|---|
1ኛ | አቶ አብርሐም ገ/አምላክ ገ/እግዚአብሄር | 7,872,875 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
2ኛ | አቶ ክፍሉ ታረቀኝ አበራ | 6,341,575 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
3ኛ | ኤን.ቲ.ኤች. ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር (ተወካይ አቶ ሚካኤል ታደሰ ካህሳይ) | 5,395,307 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
4ኛ | አቶ ወ/ገብርኤል ወዳጆ አስገዶም | 5,086,284 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
5ኛ | አቶ ሃይለ በርሄ ክንፈ | 5,067,974 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
6ኛ | ወ/ሮ ብርሃን ሃጎስ ወ/ሩፋኤል | 4,985,599 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
በተጠባባቂነት የተያዙ | |||
7ኛ | ዶ/ር ተ/ሀይማኖት ሀ/ስላሴ ተክሉ | 4,912,403 | ተጠባባቂ |
8ኛ | አቶ ገ/እግዚአብሄር ተስፋይ መርሻ | 4,066,646 | ተጠባባቂ |
9ኛ | አቶ በየነ በላይ በርሄ | 3,179,564 | ተጠባባቂ |
10ኛ | ዶ/ር ካሳ ሚካኤል ወ/የሱስ | 1,731,855 | ተጠባባቂ |
11ኛ | አቶ አረጋኸኝ ሲሳይ ገ/ወልድ | 1,251,375 | ተጠባባቂ |
12ኛ | ዶ/ር ገ/አብ ገ/እግዚአብሄር አብርሃ | 380,778 | ተጠባባቂ |
ደረጃ | የእጩዎች ሙሉ ስም | ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑ ባለአክስዮኖች ብቻ ድምፅ | ምርመራ |
---|---|---|---|
1ኛ | አቶ ቶማስ ገ/ማርያም ገ/ተንሳይ | 1,973,927 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
2ኛ | አቶ ረዘነ ሃይሉ ወ/ገብርሄል | 1,701,232 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
3ኛ | ዶ/ር ተካ ባራኺ ጎሹ | 1,639,837 | ተመራጭ የቦርድ አባል |
በተጠባባቂነት የተያዙ | |||
4ኛ | አቶ አርአያ ተስፋዬ ገ/ህይወት | 1,010,131 | ተጠባባቂ |
5ኛ | አቶ ካህሳይ ኃይሌ ገሰሰው | 936,109 | ተጠባባቂ |
6ኛ | አቶ ታመነ አለሙ ገመዳ | 324,448 | ተጠባባቂ |