Announcement

የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት የምርጫ ውጤት ስለመግለፅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ተቋማዊ አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ምልመላና ምርጫ አፈፃፀም መመሪያ” መሠረት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ቅዳሜ ጥቅምት 19 ቀን 2015 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል፡፡

በዚሁ መሠረት በእለቱ በተካሄደው ምርጫ መሠረት የጉባኤው ጽ/ቤት አባል የሆኑ ድምፅ ቆጣሪዎች፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምልመላና ምርጫ ኮሚቴ እና የሠነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ተወካይ በተገኙበት፤ በሁሉም ባለአክሲዮኖች የጠቆሙና የተመረጡ 12 እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙና የተመረጡ 6 እጩዎች በአጠቃላይ በ18 እጩዎች መካከል በተካሄደ ምርጫና የድምፅ ቆጠራ በእጩዎቹ ስም ትይዩ የተገለፀውን ድምፅ ያገኙ ሲሆን፣ በተገኘው ውጤትም፡-

በሁሉም ባለአክሲዮኖች የተመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች ብቻ የመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ መሠረት ለሚቀጥሉ ሦስት ዓመታት የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ሆነው እንዲሰሩ፣ እንዲሁም በሁለቱም ምድብ በቂ ድምፅ ያላገኙት እጩዎች በየምድባቸው እንደ ቅድመተከተላቸው በተጠባባቂነት እንዲያዙ፤ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምመላ እና ምርጫ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ የወሰነ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ሀ. በሁሉም ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙ እጩዎች ስም ዝርዝር፣

ደረጃ የእጩዎች ሙሉ ስም የባለአክስዮኖች የጋራ ድምፅ ምርመራ
1ኛ አቶ አብርሐም ገ/አምላክ ገ/እግዚአብሄር 7,872,875 ተመራጭ የቦርድ አባል
2ኛአቶ ክፍሉ ታረቀኝ አበራ 6,341,575 ተመራጭ የቦርድ አባል
3ኛ ኤን.ቲ.ኤች. ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር (ተወካይ አቶ ሚካኤል ታደሰ ካህሳይ) 5,395,307 ተመራጭ የቦርድ አባል
4ኛአቶ ወ/ገብርኤል ወዳጆ አስገዶም 5,086,284 ተመራጭ የቦርድ አባል
5ኛ አቶ ሃይለ በርሄ ክንፈ 5,067,974 ተመራጭ የቦርድ አባል
6ኛ ወ/ሮ ብርሃን ሃጎስ ወ/ሩፋኤል 4,985,599 ተመራጭ የቦርድ አባል
በተጠባባቂነት የተያዙ
7ኛ ዶ/ር ተ/ሀይማኖት ሀ/ስላሴ ተክሉ 4,912,403 ተጠባባቂ
8ኛ አቶ ገ/እግዚአብሄር ተስፋይ መርሻ 4,066,646 ተጠባባቂ
9ኛ አቶ በየነ በላይ በርሄ 3,179,564 ተጠባባቂ
10ኛ ዶ/ር ካሳ ሚካኤል ወ/የሱስ 1,731,855 ተጠባባቂ
11ኛ አቶ አረጋኸኝ ሲሳይ ገ/ወልድ 1,251,375 ተጠባባቂ
12ኛ ዶ/ር ገ/አብ ገ/እግዚአብሄር አብርሃ 380,778 ተጠባባቂ

ለ. ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑ እና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙ እጩዎች ስም ዝርዝር፣

ደረጃ የእጩዎች ሙሉ ስም ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑ ባለአክስዮኖች ብቻ ድምፅ ምርመራ
1ኛ አቶ ቶማስ ገ/ማርያም ገ/ተንሳይ 1,973,927 ተመራጭ የቦርድ አባል
2ኛ አቶ ረዘነ ሃይሉ ወ/ገብርሄል 1,701,232 ተመራጭ የቦርድ አባል
3ኛ ዶ/ር ተካ ባራኺ ጎሹ 1,639,837 ተመራጭ የቦርድ አባል
በተጠባባቂነት የተያዙ
4ኛ አቶ አርአያ ተስፋዬ ገ/ህይወት 1,010,131 ተጠባባቂ
5ኛ አቶ ካህሳይ ኃይሌ ገሰሰው 936,109 ተጠባባቂ
6ኛ አቶ ታመነ አለሙ ገመዳ 324,448 ተጠባባቂ