Announcement

ለተከበራችሁ የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) ባለአክሲዮኖች በየስማችሁ የተደለደለላችሁን አዲስ አክሲዮን እንድትገዙ የተላለፈ
የጋዜጣ ጥሪ

አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) ታህሳስ 20/2016 ዓ.ም ባከናወነው 7ኛ “አስቸኳይ” ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የማህበሩን ካፒታል ለማሳደግ ጉባኤው ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወሳል፡፡

በዚህም መሠረት ነባር ባለአክሲዮኖች የቀደምትነት መብታችሁን በመጠቀም የተደለደለላችሁን አዲስ አክሲዮኖች በአዋጅ ቁጥር 1243/2013 የንግድ ሕግ አንቀጽ 454 እና 455 መሠረት ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 11/2016 ዓ.ም ድረስ አዲስ አበባ ለምትገኙ ባለአክሲዮኖች በአንበሳ ኢንሹራንሽ ሕንፃ ዋና መ/ቤት እንዲሁም በተለያዩ ክልሎች እና አስተዳደሮች ለምትገኙ ባለአክሲዮኖች አቅራቢያችሁ በሚገኙት የማህበሩ ቅርንጫፎች ቀርባችሁ የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት የተደለደለልዎትን አዲስ አክሲዮኖች ሙሉ ገንዘብ በዋጋቸው ከፍለው እንዲያጠናቅቁ በአክብሮት እያሳወቅን፤

ባለአክሲዮኖች የተደለደለላቸውን አዲስ አክሲዮኖች ለመግዛት ሲቀርቡ ተራፊ አክሲዮኖች ካሉና ተጨማሪ አክሲዮን ለማግዛት ፈቃደኛ ከሆኑ የሚገዙትን ተጨማሪ የአክሲዮኖች መጠን በሚዘጋጀው ፎርም ላይ በመሙላት እንዲያረጋግጡ በአክብሮት እንጠይቃለን፡፡

የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ)
የዳይሬክተሮች ቦርድ

ማስታወቂያ
ለተከበራችሁ የአንበሳ ኡንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) ባለአክሲዮኖች በሙሉ

በኢ.ፌ.ድ.ሪ የንግድ ሕግ አዋጅ ቁጥር 1243/2013 መሠረት የኩባንያውን የመመስረቻ ፅሁፍ እና መተዳደሪያ ደንብ ማዋሀድ በማስፈለጉ የተዘጋጀውን ረቂቅ የተሻሻለ የመመስረቻ ፅሁፍ በኩባንያው ድህረ-ገጽ ላይ የተጫነ መሆኑን እየገለፅን፤ ያላችሁን አስተያየቶች ሆነ ማናቸውንም ግብአቶች በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት የማህበሩ ፀሐፊ ቢሮ በአካል በመቅረብ እንድትሰጡልን ወይም በሚከተለው የኢ-ሜል አድራሻ haileab@anbessainsurance.com ከአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ በፊት እንዲልኩልን በማክበር እንጠይቃለን፡፡

የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ)
የዳይሬክተሮች ቦርድ

ለተከበሩ የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) ባለአክሲዮኖች
ቀሪ ያልተካፈለ የአክሲዮን ገንዘብ(ዋጋ) እንዲከፍሉ
የተላለፈ ጥሪ፤

29/03/2016

አንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ) ህዳር 29/2011 ዓ.ም ባከናወነው 5ኛ “ድንገተኛ” ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የኩባንያውን ካፒታል ለማሳደግ ጉባኤው ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት የተደለደለላችሁን አክሲዮን ለመግዛት ፈርማችሁ በ5 ዓመት የጊዜ ገደብ ውስጥ ህጋዊ መብታችሁን ያልተጠቀማችሁ ባለአክሲዮኖች፤

ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ህዳር 29/2016 ዓ.ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ አዲስ አበባ ለምትገኙ ባለአክሲዮኖች በአንበሳ ኢንሹራንሽ ሕንፃ ዋና መ/ቤት እንዲሁም በተለያዩ ክልሎች እና አስተዳደሮች ለምትገኙ ባለአክሲዮኖች አቅራቢያችሁ በሚገኙት የኩባንያው ቅርንጫፎች በመቅረብ እንድትከፍሉ በአክብሮት እየጠየቅን፤ በተባለው ጊዜ ውስጥ ካልከፈላችሁ ግን ኩባንያው ተራፊውን አክሲዮኖች በሀራጅ ለመሸጥ የሚገደድ መሆኑን የዳይሬክተሮች ቦርድ በአክብሮት ያሳውቃል፡፡

የአንበሳ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ)
የዳይሬክተሮች ቦርድ

የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት የምርጫ ውጤት ስለመግለፅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ተቋማዊ አስተዳደር መመሪያ ቁጥር SIB/48/2019 እና የዳይሬክተሮች ቦርድ ምልመላና ምርጫ አፈፃፀም መመሪያ” መሠረት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ቅዳሜ ጥቅምት 19 ቀን 2015 ዓ.ም መካሄዱ ይታወሳል፡፡

በዚሁ መሠረት በእለቱ በተካሄደው ምርጫ መሠረት የጉባኤው ጽ/ቤት አባል የሆኑ ድምፅ ቆጣሪዎች፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምልመላና ምርጫ ኮሚቴ እና የሠነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ጽ/ቤት ተወካይ በተገኙበት፤ በሁሉም ባለአክሲዮኖች የጠቆሙና የተመረጡ 12 እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙና የተመረጡ 6 እጩዎች በአጠቃላይ በ18 እጩዎች መካከል በተካሄደ ምርጫና የድምፅ ቆጠራ በእጩዎቹ ስም ትይዩ የተገለፀውን ድምፅ ያገኙ ሲሆን፣ በተገኘው ውጤትም፡-

በሁሉም ባለአክሲዮኖች የተመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች እና ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች ብቻ የመረጡት እጩዎች ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት እጩዎች ባገኙት ከፍተኛ ድምፅ መሠረት ለሚቀጥሉ ሦስት ዓመታት የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ሆነው እንዲሰሩ፣ እንዲሁም በሁለቱም ምድብ በቂ ድምፅ ያላገኙት እጩዎች በየምድባቸው እንደ ቅድመተከተላቸው በተጠባባቂነት እንዲያዙ፤ የዳይሬክተሮች ቦርድ የምመላ እና ምርጫ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ የወሰነ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ሀ. በሁሉም ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙ እጩዎች ስም ዝርዝር፣

ደረጃ የእጩዎች ሙሉ ስም የባለአክስዮኖች የጋራ ድምፅ ምርመራ
1ኛ አቶ አብርሐም ገ/አምላክ ገ/እግዚአብሄር 7,872,875 ተመራጭ የቦርድ አባል
2ኛ አቶ ክፍሉ ታረቀኝ አበራ 6,341,575 ተመራጭ የቦርድ አባል
3ኛ ኤን.ቲ.ኤች. ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር (ተወካይ አቶ ሚካኤል ታደሰ ካህሳይ) 5,395,307 ተመራጭ የቦርድ አባል
4ኛ አቶ ወ/ገብርኤል ወዳጆ አስገዶም 5,086,284 ተመራጭ የቦርድ አባል
5ኛ አቶ ሃይለ በርሄ ክንፈ 5,067,974 ተመራጭ የቦርድ አባል
6ኛ ወ/ሮ ብርሃን ሃጎስ ወ/ሩፋኤል 4,985,599 ተመራጭ የቦርድ አባል
በተጠባባቂነት የተያዙ
7ኛ ዶ/ር ተ/ሀይማኖት ሀ/ስላሴ ተክሉ 4,912,403 ተጠባባቂ
8ኛ አቶ ገ/እግዚአብሄር ተስፋይ መርሻ 4,066,646 ተጠባባቂ
9ኛ አቶ በየነ በላይ በርሄ 3,179,564 ተጠባባቂ
10ኛ ዶ/ር ካሳ ሚካኤል ወ/የሱስ 1,731,855 ተጠባባቂ
11ኛ አቶ አረጋኸኝ ሲሳይ ገ/ወልድ 1,251,375 ተጠባባቂ
12ኛ ዶ/ር ገ/አብ ገ/እግዚአብሄር አብርሃ 380,778 ተጠባባቂ

ለ. ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑ እና ተፅእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የተጠቆሙ እጩዎች ስም ዝርዝር፣

ደረጃ የእጩዎች ሙሉ ስም ተፅእኖ ፈጣሪ ያልሆኑ ባለአክስዮኖች ብቻ ድምፅ ምርመራ
1ኛ አቶ ቶማስ ገ/ማርያም ገ/ተንሳይ 1,973,927 ተመራጭ የቦርድ አባል
2ኛ አቶ ረዘነ ሃይሉ ወ/ገብርሄል 1,701,232 ተመራጭ የቦርድ አባል
3ኛ ዶ/ር ተካ ባራኺ ጎሹ 1,639,837 ተመራጭ የቦርድ አባል
በተጠባባቂነት የተያዙ
4ኛ አቶ አርአያ ተስፋዬ ገ/ህይወት 1,010,131 ተጠባባቂ
5ኛ አቶ ካህሳይ ኃይሌ ገሰሰው 936,109 ተጠባባቂ
6ኛ አቶ ታመነ አለሙ ገመዳ 324,448 ተጠባባቂ